ዌብ (የመረጃ መረብ) በ1989 ጄኔቭ ስዊዘርላንደ በሚገኘው በቁስ ፊዚክስ ላቦራፖሪ (Paeticle Physics Laboratory) የአሁኑ የአውሮጳ ተቋም ለኒኩላር ፊዚክስ (CERN), ቲም በርነርስ ሊ የሚባል የኮምፒዩተር ባለሙያ መረጃ ለማስተዳደር የሚያስችል hypertext ተጠቅሞ ተመሳሳይነት ያላቸውን ዶኩመንቶች ማቆራኛ ከተቆራኙ(networked) ኮምፒተሮች ላይ መጠቀም የሚያስችል ሃሳብ አቀረበ። ከጓደኛው ሮበርት ኬልዩ በመሆን ንድፍ በመስራት ለግምገማ አቀረቡ። ለተወሰኑ አመታት ዌብ በጽሁፍ ላይ የተመረኮዘ መሆኑ በአለም ላይ በ1992 የነበሩት የመረጃ መረብ አገልጋዮች(web servers) ብዛት 50 ብቻ ነበር። በ1992 የመጀመሪያው ግራፊክ የሚጠቀመው ማሰሻ (Browser-----NCSA Mosaic) መምጣት ምክንያት በማድረግ ዌብም በፍጥነት ማደግ ጀመረ።
No comments:
Post a Comment